Saturday, January 12, 2013

የዚያን ሰሞን


አሁን አሁን አይኖችህ ሸሽተወኝ
ቀኔም ጠቁሮ ጨልሞብኝ
ጀንበር ጠልቃ መሻሽቶብኝ
ሆንኩኝ እንጂ ግራ የገባኝ
ያኔ ድሮ የዚያን ሰሞን
የማይ ጊዜ አይኖችህን
በብርሃንህ የፈካሁኝ
ያንተ ድምቀት ያደመቀኝ
በደስታህ ደስታ ያለኝ
ከሴት ሁሉ ተመርጬ
      አለም በጄ የሆነልኝ
ፍቅር በዝቶ የተረፈኝ
ነበርኩልህ የሞላልኝ
             የዚያን ሰሞን ወረት ይዞህ
አፍክተኸኝ በፈገግታህ
አጥግበኸኝ በቁልምጫህ
አሙቀኸኝ በዳበሳህ
አሁን አሁን ስትሸሸኝ
ሆንኩኝ እንጂ ቆሌ የራቀኝ
የዚያን ሰሞን የኔ እያለህ
አይ ነበረ በውስጥ አይንህ
የኔ አለም አንተ እንደሆንክ
ሳትቀር በፊት ወረት ይዞህ
@           @          @

No comments:

Post a Comment