Saturday, February 16, 2013

እንባዬን በዋንጫ......


በጉንጮቼ ወለል ላይ ከተረፈረፉት ዘለላዎች መሀል
………………………………………………………..አንዲቷን በጥሼ
የናፍቆቴን መጠን የብዛቱን ነገር ቀምሜ ጠንስሼ
የውስጤን ቃጠሎ የመጨስ መንደዴን በላዩ ከልሼ
……………………………………………………ይኸው ሰድጃለሁ
…………………………………………………..ይድረስህ ብያለሁ
እንባዬን በዋንጫ ሞልቼ ልኬያለሁ፡፡
አለበት በውስጡ መሻቴ ጠረንህን
አይንህን መራቤ መፈለጌ አንተን፡፡
በድምጽህ እርቀት አይሆኑ የሆነው
በመጥፋትህ ሰበብ ልቤ የቆሰለው
የኔ ያልኩት ልብህ ነውና የጨከነው
የሆንኩትን ሁሉ ሆነህ እንድታየው
እንደደራሽ ሆኖ በፈረስ ጉልበቱ ልብህን እንዲንጠው
ንዴቴን የያዘ አንኳር እንባም አለው፤
ግን አንተ ውዴ ሆይ ዋንጫውን ከሞላው
በብዛት በመጠን ልቆ የሚልቀው
ላንተ ያለኝ መውደድ ሀያሉ ፍቅሬ ነው፡፡